ድጋፉ በኮንሶ ውድ ልጆቿ ተጠናክሮና ተቀጣጥሎ ቀጥሏል!!
ታሪካዊ የጨቃ ታራ ታካ ለጎበዝ ተማሪዎች ት/ቤት ድጋፍ በኮንሶ ውድ ልጆቿ ተጠናክሮና ተቀጣጥሎ ቀጥሏል!!በሀዋሳ የሚኖረው የቀድሞ የኮንሶ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩ ውድ ወንድማችን አቶ ታክቶ ገንሾሌ የ400 ቀናት ልዩና ውድ ድጋፋቸው እና በጂንካ የሚኖር ውድ ወንድማችን አቶ ታዲዎስ ቱካኖ የ100 ቀናት ታሪካዊ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡ይህ ታላቅ መነሳሳትና ድጋፍ ልማት ማህበሩና መላው የኮንሶ ሕዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከልብ ውድ ልጆቹን ያመሰግናቸዋል!ወንድሞቻችን እጅግ በጣም ከልብ እናመሰግናቸዋለን!ታርክ በጎውን እየተመዘገበ ይገኛል፡፡ በጎ ታርክ ሰርቶ ለትውልድ ማውረስ እጅግ በጣም ትልቅነት ነው!! ይህ የተቀጣጠለው ታሪካዊ ድጋፉ የሚቆመው ትምህርት ቤቱ ጎበዝ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መላክ ስትጀምርና የታሪክ መዝገብ ቦታውን ስይዝ ብቻ ነው!ዛሬ፤ ነገም፤ ሁሌም ይቀጥላል! ልማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው!ገፃችን ከወደዱ ላይክና ሼር ያድርጉ! Like & share our page if you are interested.ጥር 16/2014 ዓ.ም
