ለኮንሶ ልማት ማህበር ውድ የንግዱ ማህበረሰብና ደጋፊዎች በሙሉ
ከሁሉም በቅድሚያ የከበረ ሰላምታችንን እያቀረብን የኮንሶ ልማት ማህበር የ2015 ዓ.ም የንግዱ ማህበረሰብ የአባልነት መዋጮ መክፈያ ወቅት ከሐምሌ ጀምሮ መሆኑን ልናስታውሳችሁ እንወዳለን::
በመሆኑም የአባልነት መዋጮ የመንግሥት የሥራ ግብር በሚትከፍሉበት ጊዜ አብራችሁ በመክፈል ወይም በኮንሶ ልማት ማህበር ዋናው ቢሮ በአካል ቀርበው አሊያም በተቋሙ የንግድ ባንክ አካወንት ቁጥር KDA MEMBERSHIP: 1000056457888 ላይ የአባልነት መዋጮዋችሁን በመክፈል ልማታዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን::
በተጨማሪም መዋጮው የተከፈለበትን ደረሰኝ ፎቶ በማንሳት(screenshot) በማድረግ በተቋሙ የፌስቡክ ገጽ ላይ በመለጠፍ አሊያም በኢሜይል konsoda1985@ gmail.com እንድትልኩ በአክብሮት እንገልጻለን::
በአባልነት ድጋፍ ብቻ የተጀመረው የካራት መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የድንገተኛ ህክምና ማዕከል ህንጻ ግንባታ ጨርሰን ሌላውን የጋራ አሻራ እንጀምራለን!
ልማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው!
